አቶ አብዲ ፀጋዬ


የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት ኃላፊ

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት በምክር ቤቱ ሁለንተናዊ የስራ እንቅስቃሴ ውስጥ ምክር ቤቱ ተቋማዊ አደረጃጀት ይዞ ስራዎችን በተቀናጀና በተሰናሰነ መልኩ ተልኮውን እንዲወጣ ምክር ቤት ጽ/ቤቱ አስፈላጊውን የሰው ኃይልና ግብዓት በማሟላት በምክር ቤቱ ሁሉን አቀፍ የስራ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የሚጠበቅበትን ተልዕኮ በትጋት እየተወጣ ይገኛል፡፡

ከዚህ ጎን ለጎን በጽ/ቤቱ ስር ያሉ ዳይሬክቶሬቶች ያለቸውን የሰው ኃይል በአቅም በክህሎት በቁ ከማድረግና የመረጃ አያያዝ ስርዓቱን ከማዘመን አንፃር የኢንፎርሜሽንና ኮሚንኬሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት በመዘርጋት የተቀናጀ የመረጃ ልውውጥ ስርዓት እንዲኖር ከማድረግ ባሻገር የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለህበረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ወቅቱ በሚጠይቀው የቴክኖሎጂ አማራጭ መረጃን በፍጠነት ለማድረስ ባስጀመርነው ዌብ ሳይት አማካኝነት የምክር ቤቱን ሁለንተናዊ የስራ እንቅስቃሴ ተደራሽ የምናደርግ መሆኑን እየገለፅኩ ለጽ/ቤታችን መሻሻልና መለወጥ እጅ ለእጅ ተያይዘን በጋራ እንድንሰራ ጥሪየን አቀርባለሁ፡፡